Ethiopianism

የኔስ ሔዋን ~ ክፍል - 1 [ከአስጌ]



የኔስ ሔዋን ~ ክፍል - 1

ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ በመብረር ላይ ባለው የህዝብ ማመላለሻ መኪና ውስጥ ገብተን (ተሳፍረን) መጓዝ ከጀመትን 1፡00 ይሆነናል።  


በጉዞው ውስጥ ሰወች የየራሳቸውን ምርጫ ተጠቅመው አንዳንዶቹ ስልካቼው ጋ ይታገላሉ። ሌሎች ደግሞ መፅሀፍትን ያያሉ። አንቻንዶች ደግሞ ተኝተዋል። 

ሰወችን ተዛውሬ ከተመለከትኩ በውሀላ እኔም የራሴን መደበርያ በመፈለግ ወደ ዋሌት ፖርሳየ እጀን በመላክ ከሆዋላ ኪሴችመዘዝ አድርጌ አውጥቼ ፎቶ ማየትና ማገላበጥ ስጀምር ከጎኔ የተቀመጠች አንድ እህቴ ( ተሳፋርይዋ ሴት ማለቴ ነው ) የማገላብጣቼውን ፎቶዎች ማየት እችል ይሆን በማለት በትህትና ጠየቀችኝ።

የልጅቱን ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር ተቀበልኩና ፎቶዎችን እያየው ወደስዋ አስተላልፈው ጀመር። ልጅቱ ሁሉንም ፎቶዎች አገለባብጣ ካየች በውሀላ ፎቶው ጋ በተደጋጋሚ አብሬያቼው ስለተነሰዋቼው ልጆች መጠየቅና ስለነሱ ማወቅ እንደምትፈልግ በፈገግታ ነገረችኝ።

እኔም የጓደኞቼን ፎቶ ተቀብየ በስነ ስርአት ለማስረዳትና ስለ ጓደኞቼ ታሪክ ለመናገር ና ለማስረዳት ያክል በትውስታ መስመር ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ከሚወስደን መኪና በሀሳብ ሰመመን ተመልሼ ባህር ዳር ገብቼ ስለነበርን የጓደኝነት ሁኔታ ማሰብና ማስታወስ ጀመርኩ። ትረካየንም በተረጋጋ መንፈስ የንዱን ጓደኛየን ፎቶ እየነካው መናገር ጀመርኩ።

ይሄ ጓደኛየ ብርሀኑ ይባላል እድሜው 17 ይሆነዋል። የ10ኛ ክፍል ተማሪ ነው። ይሄ ልጅ ሴት በጣም ነው እሚወደው። ግን ማናገር ስለሚፈራ ወድዋት ነው እሚቀረው እንጅ እስዋ ካልፈለገች እሱ አያናግራትም። ይሄኛው ደግሞ ዳንኤል ይባላል። 

10ኛ ክፍል ካጠናቀቀ 2አመት ሆኖታል። ሴት ናት የተባለች አታመልጠውም። መልክ ሀብት ምናምን አይልም ብቻ ግን ተቀምጣ ትሸናለች ከተባለ ለሱ ምርጫው ነች። ግን ሴቶች ሁሉ እንደሱ ስለሚመስሉት በጣም ነው የሚጠላቸውና የሚጠነቀቃቼው። ያለ ኮንዶም በፍፁም ሴክስ አያደርግቼውም።  

ይሄ ደግሞ መልካሙ ይባላል። የዩንቨርስቲ ተማሪ ነው በቀጣይ አመት ይመረቃል። መልካሙ በትምህርቱ በጣም ጎበዝ ነው። ግን አንዴ ወደየልጅነት 11ኛ ክፍል እንዳለፈ አቋርጦት ነበር። ምክንያቱም ፍቅር ነው። በጣም የሚያፈቅራትና የምታፈቅረው የነበረች ፍቅሩ አሜሪካ ልውሰድሽ ብሎ አታሎ በተዋት ሰውየ የከዳችውን ማስቴን ለመርሳት በሚል ምክምያት ነበር ያቋረጠው። 

መልኬ በትምህርቱየያዘው በጣም ጎበዝ ሰለነበር ቤተሰቦቹና አንዳንድ መካሪወቹ ጉትጎታ ማስቴን እረስቶ ወደ ትምህርቱ ተመልሶ አሁን ሊመረቅ አመትና ቀጣይ 1አመት ብቻ ነው የቀረው ግን መልኬ ከዛህን ጊዜ ወዲህ ሴት የተባለች እርሜ ብሎ ተቀመጠ።  

ሴት የተባለች ባጠገቡ ባታልፍ ደስታው ነው። አይደለም የሰውና የእንስሳም ቢሆን አትለፉብኝ የሚል ነው እሚመስለኝ።
ኦ !! ይቅርታ ስለኔ ሳልነግርሽ እኔ ያው እንደምታይኝ ለማያቁኝና ለሚጠሉኝ ነው እንጅ የማላምረው ለእናቴ ወርቅ ነኝ። እየቀለድኩ እንዳይመስለሽ ከምሬ ነው። ከወርቅም የበለጠ ወርቅ እንደሆንኩ ደጋግማ ስለምትነግረኝ ነው። 

እናትዬ እወድሻለሁ ግን ግን የማልዋሽሽ ነገር ቢኖር የመልኬ የድሮ ፍቅረኛው ጋ ተልኬ ስሄድ ምን ትለኝ ነበር መሰለሽ "አንተ የሆንክ አስፓልት ፊት" ምን አርጊ ነው እምትሉኝ። ስትለኝ እኔም ተልኬ ነው ብየ ንግግሬን ልጀምር ስጣደፍ ትቀጥልና 

ያንን መናጢ ደሀ ጓደኛህን ስትለው ድሀ ሲሰራና ሲማር እንጅ ሲያፈቅር አያምርበትም በለው ትልና አንተ ደግሞ እሱን ቅ/ሚካኤል የደበደበውን የሚመስለውን ፊትህን በዚህች መኪና ሳልገጭልህ እያለች መኪና እንደተገዛላት በጠቋሚ እጣትዋ ስታሳየኝ በንግግሯ ተናድጄ ወደ መጣውበት እበራለሁ።

አሁንም ይቅርታ ልጠይቅሽ ይቅርታ ፣አሽና አመሰግናለሁ እሚባሉት ቃላቶች ለሰው ልጅ አስፈላጊ ስለሆኑ ልንጠቀማቼው ይገባል። ስሜ ♥ናትናኤል ይባላል። እኔ ከጓደኞቼ አስበልጨ የምደወው እዮብን ነው። 

ምክናቱም ዳንኤል ሴትን ልጅ በመበቀል ስራ ተጠምዶ እንዲያቆም ስንጠይቀው መልካሙን ያሳመመችው ሴት ልጅ መልሳ አክማ እስክታድነው ድረስ ሴትን አልምርም እያለ ሴቶችን በማጭበርበር ና በመቅረብ ከሚያገኛት ሴት ጋ ሴክስ ያደርጋል። እኔም ይህንን ተግባሩን አልወድለትም። 

መልካሙ ደግሞ እፆታዋ ሴት የሆነች ሁሉ ተጎድታ ፣ታማ፣እቦዋት፣ወድቃ ተሰብራ፤ ወይም ወንድም ቢሆን እባክህንችእርዳኝ ብሎት ሚስቴ ልትሞትብኝ ነው ወይ እህቴ ወይ ፍቅረኛየ ካለው እንደቆመ ብትሞት ነው እሚመርጠው እንጅ አይረዳውም። ለሱ ሁሉም ሴቶች አንድ ናቼው። 

ብርሀኑም አንድ ችግር አለበት። የሴቶችን የማይቀርበው የተከዳውን መልኬን በማየትና በሚያተራምሰው ዳንኤልን ሲያይ ከዳኒ ጋ የሚተኙት ሴቶች ሁሉ እንደ ዳኒኤል ናቼው ብሎ ስለሚያስብ ነው። እናም እዮብም ከነሱ እማስበልጥበት ምክንያት ይሄው ነው። 

እዮባ አንድ ምርጥ አባባል አለችው። መልካም ሴት በትዕግስት እንጅ በፍለጋ አትገኝም ብሎ ስለሚያምን ነው። እኔ ግን አንደሱም አይደለሁም። እስከ 8 አመቴ ድረስ ገጠር ሲሆን ያደኩት ከዛ በ1988 ጥር17 ባህር ዳር ከተማ ገባን።

በዚህ ወቅት የኤች አይቪ በሽታ እየተስፋፋና እየተነገረለት የነበረበት ወቅት ሰለነበር አባቴ ሴት የምትባል ንገር ቀትቤ ካወራሁና አብሬያት ከተቀመጥኩ ኤች አይቪ ይዞኝ እንደምሞትና ከቤትም እንደሚያባርረኝ በሰፊው ይሰብከኝ ሰለነበር ቃሉን ስላጓድል እስከ 7ኛ ክፍል ድረስ በፍቅርና በደስታ ቤተሰቤ ጋ እያሳለፍኩ ባለውበት ላይ 7ኛ ክፍል እንደገባው አንድ አዲስ ነገር ተከሰተ.. ........

ክፍል 2 ይቀጥላል

No comments